ቀኖቹ ተቆጥረው ወራት ይሰፍራሉ፣
ወራትም ተቆጥረው ዓመት ይሞላሉ፣
እንዲሁም ዓመታት ዘመን ይለያሉ።
የሚገርም እኮ ነው እንዲህ በድንገት፣
ይቺ ጊዜ እሚሏት አላት ብልሃት፣
ይዛ ትመጣለች አዲሱን ዓመት፣
ከተፍ ትላለች ሰው ሳይነቃባት።
እራሴን ስጠይቅ በዚህ አዲስ ዓመት፣
ቁጥር ጨመረና ምንድነው የኔ እድገት?
አዲስ ዓመት ቢሆን ልክ እንደ መስታዎት፣
ምን አንዳደረኩኝ ልኩን የማይበት፣
እያልኩ ጠየኩት እራሴ በድንገት፣
መቼ ይሆን እኔ ለውጦች የማይበት።
Error: No site found with the domain 'mail.mejemer.com' (Learn more)